በክልሉ በበጀት ዓመቱ 11 አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደሥራ ገብተዋል – አቶ አሻድሊ ሀሰን

‎****************

‎(አሶሳ፣ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2017 በጀት ዓመት 11 አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደሥራ መግባታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።

‎መንግስት ህብረተሰቡ የሚያነሳቸው ጥያቄዎች ለመመለስ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን የተናገሩት አቶ አሻድሊ፣ የአርሶ-አደሩን ሕይወት ለመቀየር የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

‎በ2017 በጀት ዓመት 14 የመስኖ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ታቅዶ 11 አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደሥራ መግባታቸውን ጠቁመዋል።

‎የክልሉ መንግሥት የፕሮጀክቶችን አፈጻጸም ጥራትና ፍጥነት ማሻሻሉን ተናግረው፤ ለአብነትም የጸንጸሃሎ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክት በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ መጠናቀቁን ተናግረዋል።

‎አርሶ-አደሩ የተጠናቀቁ የመስኖ ፕሮጀክቶችን ተጠቅሞ ከክረምት እስከ በጋ በማምረት ምርታማነቱን ሊያሳድግ እንደሚገባም አቶ አሻድሊ ገልጸዋል።

#የቤኒሻንጉል_ጉሙዝ_ክልል_የመንግሥት_ኮሙኒኬሽን_ጉዳዮች_ቢሮ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *