የዳይሬክተሩ ተግባርና ኃላፊነት

  • የክልሉ የገጠር ልማት ፖሊሲዎች  ስትራቴጂዎችና ስልቶች በክልሉ ውስጥ ያስፈፅማል፣ይህንኑ መሠረት አድርጎ በክልሉ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር የተገናዘቡ የፖሊሲ ሃሳቦችን ያመነጫል ሲፈቀድም በሥራ ላይ እንዲውል ያደርጋል፣
  • የግብርና ምርት ምርታማነትን ለማሳደግ ከምርምርና ከማሰልጠኛ ማዕከላት ጋር ተቃናጅቶና ተሳስሮ ይሰራል፣ ድጋፍም ይሰጣል፣
  • የግብር እንቨስትመንት እንዲስፋፋ ያበረታታል፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ሙያዊ እገዛና ክትትል  ያደርጋል፣
  • አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችና አሰራሮችን ለተጠቃሚው ህዝብ ለማስረጽ የኤክስቴንሽን አገልግሎት በሁሉም የክልሉ አካባቢች እንዲሰጥ ያደርጋል፣ ምርታማነት እንዲያድግ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፣
  • አግባብ ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር ለግብርናና ገጠር ልማት መፋጠን አስፈላጊ የሆኑ የእርሻ ሣሪያዎች፣ ፀረ-ተባይ ኬሚካሎች፣የእንስሳት መድሃኒት፣የብድር አገልግሎት እና ሌሎች የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶች አገልግሎት እንዲዳረስ ጥረት ያደርጋል፣
  • ቢሮው በስሩ ለሚገኙ የግብርና ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ፣ የመከናይዜሽንና  የገጠር ቴክኖሎጂ ኤጀንሲና ማዕከላትን ለግብርናው ዘርፍ አገልግሎት ያደራጃል ፣ ያስተባብራል ፣ ይቆጣጠራል፣
  • የክልሉ የተፈጥሮ ሃብት በአግባቡ እንዲጠበቅ የተዘረጋ የአሰራር ሥርዓት ተግባራዊ እንዲሆን ስልት ቀይሶ ይሰራል፣
  • የነባር ብሄረሰብ ግርብርና ዘይቤ ማጥናት የተፈጥሮ ሀብቱን አባበቅና ምርታማነትን ባገናዘበ መልኩ የግብርና ዘዴ ስልት በመቀየስ ብሔረሰቦች ከዘመናዊው  የግብርና ቴክኖሎጂ ጋር እንዲተዋወቁ የልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋል፣
  • የደን ምርምርና ልማት ለማስፋፋት የሚያስችሉ የምርምር፣የግብዓት ማባዣ፣የደን ዕፅዋት ዘር ጥራት ቁጥጥር  ማዕከላት እና ላቦራቶዎችን  ያቋቁማል፣ያስተዳድረል፣
  • የክልሉ አርሶ አደሮችን የምግብ ዋስትና የሚረጋገጥበትን መንገድ በመደገፍ  ተግባራዊ  ያድርጋል፣
  • የአርሶ አደሩ ምርቶችን ሳያባክኑ ገበያ የሚገኙበትን ሁኔታ ያመቻቻል የገበያ ትስስር ሊፈጥር የሚችሉበትን  ስልት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመንደፍ ተግባራዊ እዲሆኑ ያደርጋል፣
  • ለአርሶ አደሩና ለግል ባለሃብቱ የሚሰጥ የዘርፍ የኤክስቴንሽን አገልግሎት ቀልጣፋና ጥራት ያለው፣ተደራሽና ውጤታማ እንደይሆን ሥርዓት ይዘረጋል፣ተግበራዊ ያደርጋል፣
  • የግብርና ልማትን ለማስፋፋት የሚረዱ ሊሎች ተግባራትን ያከናውናሉ፣
  • የንብረት ባለቤት ይሆናሉ፣በስሙ ውል ይዋዋላል፣ይከሳል ይከሰሳል፣
  • ዓላማውን ለማስፈፀም የሚችሉ ሌሎች ተዛማች ተግባራትን ያከናውናል፡፡