የዕቅድ ዝግጀት ክትትል ግምገማ ዳይሬክቶሬት

  1. የመሥሪያቤቱን ዓመታዊ እቅድ በማዘጋጀት፣ አፈጻጸሙን በመከታተል፣ በመገምገም፣ የእቅድ ዝግጅትና አፈጻጸምን የሚያሻሽሉ ጥናቶችን በማካሄድ የመሥሪያ ቤቱን የእቅድ አፈጻፀም ውጤታማ እንዲሆን ማስቻል ነው፡፡ 
  2. የተቀቋሙን ዓመታዊ እቅድ ያዘጋጃል፣ ይከልሳል፣ ያሻሽላል፣ ለበላይ ኃላፊ አቅርቦ ያጸድቃል፣
  3. የተቋሙ ስትራቴጂክ እቅድ ሲዘጋጅና ሲከለስ  አስፈላጊውን ግብአት ያሰባስባል፣ ያዘጋጃል፣ የእቅድ ዝግጅቱ ላይ ሙያዊ ድጋፍ ይሰጣል፤
  4. አዳዲስ የፖሊሲ ሀሳቦች ሲቀርቡ ከተቋሙ ኃላፊነትና ተግባር ጋር የሚዛመዱ መሆናቸውን ያረጋግጣል፣ አስተያየት ይሰጣል፣
  5. ለእቅድ ማስፈጸሚያ የሚሆን የበጀት ፍላጎት ያዘጋጃል፣ ይጠይቃል፤ የተፈቀደውን በጀት ለየሥራ ክፍሎች ይደለድላል፣
  6. የሌሎች ሥራ ክፍሎችን ዕቅድ ዝግጅት ላይ ሙያዊ ድጋፍ ያደርጋል፣ የምክር አገልግሎት ይሰጣል፣
  7. በእቅድ ዝግጅት ክትትልና ግምገማን በሚመለከት ለሥራ ክፍሉ ባለሙያዎችና ሌሎች እንደ አስፈላጊነቱ ስልጠና ይሰጣል፡፡
  8.  የመሥሪያ ቤቱን የበጀት አጠቃቀም በእቅድ መሠረት መሆኑን ይከታተላል፣ በእቅድና በበጀት አጠቃቀም የሚከሰቱ የአፈጻጸም ችግሮችን በመለየት የሚፈቱበትን የውሳኔ ሀሳብ ለኃላፊው ያቀርባል፣
  9. በመሥሪያ ቤቱ የተዘጋጀውን ዓመታዊ እቅድና በጀት አፈጻጸም ይከታተላል፤ ይገመግማል፤ ግብረ-መልስ  ይሰጣል፤
  10. የተመደበው በጀት በፕሮግራሙ መሠረት ለተፈለገው ሥራ መዋሉን ይከታተላል፤ ችግር ሲያጋጥም የማስተካከያ እርማጃ እንዲወሰድ ያደርጋል፤
  11. የበጀት እጥረት ሲያጋጥም የበጀት ምንጭ የሚገኝበትን አማራጭ ሀሳብ ለኃላፊው ያቀርባል፤ የበጀት ዝውውር ሲፈቀድ ተግባራዊ ያደርጋል፤ አፈጻጸሙን ይከታተላል፣
  12. ከጥናት ከግምገማና ወቅታዊ ጉዳዮች የመነጩ መረጃዎችን ጥልቅ ትንተና በማካሄድ ተግባራዊ እንዲሆን ያደርጋል፣ አፈጻጸሙን በመከታተል የውሳኔ ኃሳብ ለበላይ ኃላፊው ያቀርባል፣
  13. የእቅድ ዝግጅት ሥራ የሚሻሻልበትን ሁኔታ በተመለከተ ጥናት ያደርጋል፣ ምርጥ ተሞክሮዎችን በማሰባሰብ ይቀምራል፣ ለውሳኔ ያቀርባል፣
  14. የእቅድ አፈጸጻምን ወቅታዊ ሪፖርት ያዘጋጃል፤ ለሚመለከተው አካል ያቀርባል፡፡
  15. መረጃ ሥራ አማራር
  16. ተለይተው የተሰጡ የመረጃ ምንጮችን በዝርዝር ይይዛል፣
  17. ከመረጃ ምንጮቹ መረጃውን ይሰበስባል፣ይለያል፣
  18. የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎችን ይቀይሳል፣   
  19. የተሰበሰቡ መረጃዎች በቅጹ መሰረት ስለመሞላታቸው ያመሳክራል፣
  20. የተሰበሰቡ መረጃዎችን ለማደረጃት በሚያመች መልኩ ዝግጁ ያደርጋል፣
  21. ከመረጃ አሰባሰብ እስከ ጥንቅር ያሉትን ተግባራት ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራር ለማድረግ እንዲሁም  ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሄ  ለመስጠት በሚደረጉ ጥናቶች ላይ ይሣተፋል፣
  22. የተጠናቀሩ መረጃዎች አንዲተነተኑ ያደርጋል፣
  23. መረጃዎቹ በአግባቡ መተንተናቸውን በማረጋገጥ ለቅርብ ኃላፊው ያቀርባል፣
  24. በተተነተኑ መረጃዎች ላይ ከኃላፊው በሚሰጥው ግብረ መልስ መሠረት አስፈላጊውን ማስተካከያ ያደርጋል፣
  25. የሥራ ክንውን ሪፖርት ያቀርባል፣
  26. የኔትወርክ አስተዳደር
  27. ymS¶Ã b@t$ ytlÆ y|‰ KFlÖC GNß#nT XNÄ!ÃdRg# b¸zrU yn@TwRK m\rt L¥T _ÂT §Y mr©ãCN ÃsÆSÆL½ _Ât$ §Y YútÍL½
  28. yn@TwRK m\rt L¥T ydrsbTN yt&KñlÖ©! dr© Yk¬t§L½
  29. b|‰ §Y Ãl# yn@TwRK m\rt L¥T XRS bRS y¸ÃStúS‰cW :QìC s!zU° q§L |‰ãCN b¥kÂwN YútÍL½
  30. bn@TwRK m\rt L¥T ZRU¬ና bn@TwRK WS_ Ãl#TN yGNß#nT s!StäC |‰ §Y YútÍL½
  31. ሲቪል መሃንዲስ
  32. የግንባታ ፕሮጀክቶች ቴክኒካዊ አፈፃፀም ይከታተላል፣ ይገመግማል፣ የአፈፃፀም ሪፖርት ያቀርባል፣
  33. የግንባታ ሥራዎች አግባብ ያላቸውን ህጎች፣ ደንቦች፣ ስታንዳርዶችና የአፈፃፀም መመሪያዎች  ጠብቃው መሠራታቸውን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣
  34. በመስክ ለሚፈጠሩ የኮንስትራክሽን ችግር መፍትሄ ይሰጣል፣ ከአቅም በላይ የሆኑ ችግሮች ሲያጋጥሙ ሪፖርት ያደርጋል፣
  35. ግንባታው ሲጠናቀቅ የመጀመሪያና የመጨረሻ ደረጃ ርክክብ ይፈጽማል፣