1. የሥራ መደቡ ዓላማ፡-
የተቋሙን የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ሥራዎች በፋይናንስ ደንብና መመሪያ መሠረት እየተከናወኑ መሆናቸውን መመርመርና የኦዲት ሪፖርት ማዘጋጀት
2. የሥራ መደቡ ውጤቶችና ተግባራት
ውጤት 1፡ የኦዲት ተግበራትን ማከናወን፡፡
የኦዲት ፕሮግራም ያዘጋጃል፡፡
የፋይናንስ አጠቃቀም አዋጆችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን የጠበቀ መሆኑን በፋይናንሺያል ኦዲት ያረጋገረጣል፣
የስጋት አካባቢ የዳሰሳ ጥናት ያካሒዳል፣ በጥናቱ ውጤት መሰረት የኦዲት ፕሮግራም ያዘጋጃል፣
መ/ቤቱ አላማውን ከግብ ለማድረስ የሚከተለው የሥራ አፈጻጸም ስልት ኢኮኖሚያዊ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ መሆኑን ለማረጋገጥ የክዋኔ ኦዲት ያካሒዳል፣
በተደደሰባቸው የኦዲት ግኝቶች ላይ የኦዲት ሪፖርት በማዘጋጀት ለኃላፊው ያቀርባል፣
ውጤት 2፡- ክትትልና ድጋፍ ማድረግ
የኦዲት አስተያየት የተሰጠባቸውን ጉዳዮች ላይ ክትትል ያደርጋል፡፡
ተግባራዊ ላልተደረጉ የእርምት እርምጃዎች ተፈጻሚ የሚሆኑበትን የመፍትሄ ሐሳብ ያቀርባል፣
ለተቋሙ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች የምክር አገልግሎት ይሰጣል፣
ለውጭ ኦዲተሮች አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል፣
