የኩርሙክ ወረዳ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ በኩርሙክ ወረዳ የተረጂነት ቅነሳ ስራ ለማከናወን በ8 ሄክታር ማሳ ላይ ያረፈ ማሽላና የሌማት ቱሩፋት ስራ የመስክ ምልከታ አደረጉ
(ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም)
የኩርሙክ ወረዳ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ በኩርሙክ ወረዳ የተረጂነት ቅነሳ ስራ ለማከናወን በ8 ሄክታር ማሳ ላይ ያረፈ ማሽላና የሌማት ቱሩፋት ስራ የመስክ ምልከታ አደረጉ።
የኩርሙክ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ዩሱፍ ኡዳ ቋሚ ኮሚቴው በወረዳ ደረጃ የተከናወኑ የሌማት ቱሩፋት መስክ ምልከታ በማድረግ የቀጣይ ተኩረት አቅጣጫ እንዲያስቀምጡ ነው ብለዋል።
የወረዳው ግብር ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብዱልከሪም ዮሚድ በበኩላቸው መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በወረዳው የምርትና ምርታማነት ስራ እና የሌማት ቱርፋት ስራ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግሯል።
አቶ አብዱልከሪም በወረዳ ደረጃ በ8 ሄክታር ማሳ በዘር የተሸፈነ ማሽላ፣የእንሰሳት እርባታ ፍየልና ቤግ በዛሬው ዕለት ምልከታ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ በየ3ወሩ 500 ዶሮ ለማስገባት እና የንብ ቆፎ ቦታዎች ዝግጁ መደረጋቸውን ገልጿል።
የኩርሙክ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከማል መሀመድ በሌማት ቱሩፋት የተከናወኑ ስራዎች እጅግ አበረታች እና ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን ተናግሯል።
አስተዳዳሪው አክለው አሁንም ቀሪ ስራዎችን በመስራት እና በሟሟላት ወረዳውን በሌማት ቱሩፋት ሞዴል በማድረግ ለጉብኝት ምቹ እናደርጋለን ብለዋል።

